Sunday, February 24, 2019

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ተማሪዎች 10ኛ ዙር ምረቃ እና የጥርስ ህክምና ተማሪዎች 2ኛ ዙር ምረቃ በደማቅ ሁኔታ አስመርቅዋል።

                                                                                                                                                       
 መቐለ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ተማሪዎች 10ኛ ዙር ምረቃ እና የጥርስ ህክምና ተማሪዎች 2ኛ ዙር ምረቃ  ቅዳሜ የካቲት 16-2011 ዓ/ም  በደማቅ ሁኔታ አስመርቅዋል።

ዩኒቨርሲቲው በአጠቃላይ 376 ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን ከእነዚህ መካከል 245 በመጀመርያ ዲግሪ (ዶክትሬት)፣ 78 በድህረ-ምረቃ፣ ስፔሻሊቲ በተለያዩ የህክምና ዘርፎች ያስመረቀ ሲሆን ከአጠቃላይ ተመራቂዎች 97 ሴት ተመራቂዎች ናቸው።
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት የኢፌዴሪ የህ/ተ/ም/ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ሂወት፣ አዳዲስ እና ነባር የቦርድ አባላት በምርቃት ስነ ከስርዓቱ ተገኝተው የእንኳን ደስ አላቹሁ መልእክታቸው ያስተላለፋ ሲሆን  መቐለ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላት፣ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ስራ ሃላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረስብ እና ውድ የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኘበት የምርቃት መርሃ  ግብሩ በደማቅ ሁኔታ ተካሂድዋል።
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስ አላችሁ እያለ መልካም የስራ ዘመን ይመኛል።
            ለካቲት 16፣2011ዓ.ም






No comments:

Post a Comment